የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የልደታ ክ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል የክፍለ ከተማው ማህበረሰብ እንዲሁም የአስተዳደሩ ፅ/ቤቶች በህግ ንቃተ ህሊና ዙሪያ፤ የህግ ምክር ድጋፍ እና በፍትሀ ብሄር ክርክር የህዝብና መንግስት ሀብት ጥቅም ማስጠበቅ ሲሆን ህግን ጠንቅቆ አለማወቅ ሊያስከትል ከሚችል ጉዳት ማህበረሰቡን እና አስተዳደሩን ለመጠበቅ በህግ አግባብ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህም በርካታ ሀብትና ንብረት አለአግባብ እንዳይባክን ሰፊ ስራ ተሰርቷል፡፡
ወቅቱን ያማከለ የህግ ግንዛቤ መሰረት በማድረግ በብሮሸር፤ በሰሌዳ መፅሄት፡ በራዲዮ እንዲሁም በቴሌቪዥን እና በአዲስ ልሳን ጋዜጣ የህግ አምድ በማውጣት ለክ/ከተማው እና ለከተማ አስተዳደሩ ግንዛቤ የሚሰጥ ሲሆን በተጨማሪም የህግ ንቃተ ህሊናን በማሳደግ ደረጃ በተለያየ ጊዜ መጠይቆችን በመበተን እና ማህበረሰቡ ሊያውቀው ይገባል ተብሎ የሚታሰበውን የህግ ጉዳዮች የማስጨበጥ ስራ ሰርተናል፡፡ በመንግስት ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 87/2017 ላይ፤ የቤት አከራይ ተከራይ አዋጅ 1320/2016 አዋጅን እና ሌሎችም ተጨባጭ ብዙ የሚባሉ የህግ ግንዛቤ ማሳደጊያ መድረኮችን በማዘጋጀት በተለይ የህግ ንቃተ ህሊና የማሳደግ ስራ ሰርተናል፡፡... ተጨማሪ ያንብቡ
አቶ ወርቁ ከተማ , የልደታ ክ/ከተማ ፍትሕ ጽ/ቤት ኃላፊ


